የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ሁለገብ ጥረት የሚያግዝ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰራ የሃገሪቷን የልማት ማዕከላትን የሚያስተሳስርና ከጎረቤት ሃገሮች ወደቦች ጋር የሚያገናኝ ዘመናዊ የባቡር መሠረተ ልማትና አገልግሎት ተገንብቶ እና ብቁ የባቡር ኩባንያ ሆኖ ማዬት::
በሀገራችን እየታየ ያለው ኢኮኖሚዊ እድገት ከፍተኛ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት የሚፈልግ በመሆኑና የንግድ ፍሰቱን ከተለያዩ የልማት ኮሪደሮች ጋር ለማስተሳሰር እንዲሁም አማራጭ ወደቦችን ለመጠቀም በተለይ የባቡር ትራንስፖርት ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡
የባቡር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ግንባታ የሀገራችንን የትራንስፖርት ዘርፍ ለማሳደግ ከሚደረጉ ወሳኝ ስትራተጂያዊ ልማቶች ውስጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ነው፡፡
ለዚህም ነው የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በሀገሪቱ የባቡር መሰረተ ልማት ግንባታን በማስፋፋት የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 141/2000 ህዳር 20/2000 ዓ.ም እንዲቋቋም የተደረገው፡፡ ይህንን ተልዕኮው እውን ለማድረግም የተለያዩ ፕጀክቶችን ቀርፆ መሠረተ ልማቱን እየዘረጋ ይገኛል፡፡
የባቡር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ግንባታ የሀገራችንን የትራንስፖርት ዘርፍ ለማሳደግ ከሚደረጉ ወሳኝ ስትራተጂያዊ ልማቶች ውስጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ነው፡፡
CEO
Previous CEOs
How can we help you?
Contact us at the Ethiopisn Railway Corporation Headoffice or submit a business inquiry online
ራዕይ
የልማት ማዕከላትን የሚያስተሳስር ከጎረቤት ሀገራትና ወደቦች ጋር የሚያገናኝ የባቡር መሠረተ ልማት ተዘርግቶና ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት በሀገሪቱ ተስፋፍቶ ማየት
ተልዕኮ
በሀገሪቱ ዘመናዊ የባቡር መሠረተ ልማት መገንባት እና የመንገደኞችና የጭነት የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት
እሴቶችና መርሆዎች
- ሰው
- ደንበኛ
- የቡድን ስራ
- ፈጠራ
- ጥራት
- አካባቢ
How we work
Look for some of our projects